Select Page

ራዕይ


ምዕራብ አዲስ አበባ መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በቃሉና በመንፈሱ
የተለወጡና የጽድቅ ተጽዕኖ የሚያመጡ በሳል ደቀመዛሙርት መፍለቂያ ሆና ማየት ( ዮሐ.158 ፤ ማቴ.51315 281820)፡፡

ተልዕኮ

ወንጌልን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል መስበክ፣ ማስተማር ፣ሁለንተናዊ አገልግሎት
መስጠትና ለጌታ ምጽዓት የተጋጁ በሳል ደቀመዛሙርትን ማፍራት ( ማር.1615 ፤ማቴ.281820 51315 2442 44 2513 ፤ፊል.32021፤ቆላ.128)

ዓላማ

  • ንጌልን ለአካባቢያችን ህብረተሰብ ማድረስ
  • ያመኑትን በእግዚአብሔር ቃል ማነፅ
  • አማኞች በተቀበሉት ስጦታ ማገልግል
  • ሁለንተናዊ አገልግሎት ማበርከት
  • በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በተለወጠ ህይወት ጌታን ማምለክ

ን  ር  ው፡፡

የእገልግሎት ዘርፎች

የትምህርት አገልግሎት ዘርፍ

የልማት አገልግሎት ዘርፍ

የልጆችና ወጣቶች ልማት ፕሮጀክት (ኮንፓሽን)

ጋብቻ እና ቤተሰብ ማማከር ዘርፍ

የወንጌል ስርጭት ዘርፍ

የእረኝነት አገልግሎት ዘርፍ

የልጆች እና ወጣቶች ዘርፍ

የዲያቆን አገልግሎት ዘርፍ

የወንጌል ስርጭት ዘርፍ

ዕሴቶቻችን

እምነት

( እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት ስለማቻል) ዕብ.11139፣ዕብ.116

ቅድስና

(በተቀደሰ ሕይወት መኖር፤(በኑሮ ሁሉ) ያለ ቅድስና እግዚአብሔርን ማየት
ስለማይቻል) 1.ጴጥ.11516፤ዕብ.1214

ፍቅር

(ለእግዚአብሔር፤ለእርስ በርስ፤ላልዳኑት የምናሳየው መታወቂያችንም
ስለሆነ) ማር1230፤ዮሐ.1334351ኛቆሮ.1317

ይቅርታ

( ልባዊ፣እውነተኛና እግዚአብሔር የሚቀበለው) ማቴ.614፤ማር.1125 26፤ኤፌ.432

አንድነትን መጠበቅ

(ክርስቶስ በቤዛነት ሞቱ የመሠረተውን የክርስቶስን
ቤተክርስቲያን አንድነት በትጋት መጠበቅ (መዝ.13313፤ኤፌ.43ቆላ.315፤ሮሜ.1556፣የሐ.172022) ፡፡

ሕብረት

( ክርስቶሳዊ ቤተሰብነትን ለማጠናከር(በህብረት ፀጋ መከፋፈል) መፀለይ፤በህብረት ቃሉን መማር፤በህብረት ማገልገል፤ለመተናነጽ፤ ለመተዋወቅ፤ለመደጋገፍ ለመሸካከም፤ጌታን ለማክበር፤)
የሐዋ.242፤ዕብ.102425

ሎሌአገልጋይነት

(ሕያዋን የመሆናችን ማሳያ ነው፡፡ ማንነታችን ነው፡፡ ባለ አደራነታችንን በመገንዘብ ከእግዚአብሔር በተቀበልነው ሥጦታ ሁሉ ቤተክርስቲያንን በማነጽና በማሳደግ እግዚአብሔርን ማክበር) ሮሜ.1268 1ኛቆሮ.14261ኛጴጥ.410112ኛቆሮ.518

ምስክርነት

ለወንጌል የአምባሳደርነት ኃላፊነታችንን በቃልና በኑሮ በየትኛውም ጊዜና ሥፍራ መወጣት (ማቴ.10323328÷1920፣የሐዋ.182ኛቆሮ.51820…አጀንዳ 2819)

ፀሎት

የአባትና የልጆቹ መነጋገሪያ አንዱ መንገድ ነው፡፡ የልጅነት ሥልጣናችንን/ መብታችንን የምንለማመድበት መንገድ ነው (ዮሐ.1÷12፣ማር.14÷36፣ሮሜ 8÷15፣ገላ.4÷6)፡፡
እግዚአብሔር እኛን ልጆቹን እንድንጸልይ ይፈልጋልእንድንጸልይ አዝዞናል፡፡ፀሎት የእኛን አለመቻል፤እግዚአብሔርን ሁሉን መቻል ማመናችንን ማሳያ (ሉቃ.18÷1፣ቆላ.4÷21ተሳ.5÷171ጢሞ.21)

መታዘዝ

ለእግዚአብሔርና በሕይወታችን ላይ ባለሥልጣን ለሆኑት ሁሉ እንደ ቃሉ ታዛዥነታችን
መረጋገጥ አለበት (1ሣሙ.1522231ኛቆሮ. 16÷16፤ኤፌ. 6÷1 ቆላ. 3÷1820፤ዕብ.
13÷171ጴጥ. 2÷1418….)

ፍትሃዊነት/አለማድላት

ሁሉን በእኩል ዐይን ማየት፣በእኩል ማስተናገድ ምክንያቱም
አባታችን አድልዊ አይደለም (ዘጸ.23÷1367፤ዘዳ.1÷16 1710÷1716÷1920፤ኢዮ.34÷19፣ሮሜ 2÷11፣ገላ.2÷6ኤፌ.6÷9)

በመንፈስ ቅዱስ ኃይል መሞላት/መጋል

(በምንኖርበት በዚህ ብልሹ ዓለም ውስጥ ለወንጌል እውነት መኖርና ማገልገል ሚቻለው
መንፈስ ቅዱስ ርዳታ አመራር ብቻ ስለሆነ ነው፡፡)
ዘካ.46፤ሉቃ.2449የሐዋ.18ሮሜ1411ገላ.51622.518.

አምልኮ

(በግልና በጋራ ለተገለጠልን አምላካዊ ማንነቱ፤ ወደር ለሌለው ማዳኑ፤ቀጥር ሥፍር
ስለሌለው ውለታው በሁሉም ሥፍራና ጊዜ የምንሰጠውን
ስግደት፤ውዳሴ፤አድናቆት፤ምስጋና፤መታዘዝ፣መገዛት፤አክብሮትና ፍጹም መሰጠትን የሚያመለክት
ምላሽ ነው) መዝ.145147፤ዕብ.12281313 ዮሐ.424

ሁለንተናዊ አገልግሎትን ማበርከት

(ሙሉውን ሰው ማገልገል፤ጩኸታችን እንዲሰማ የሌሎችን ጨኸት መስማት፤በቃልና በተግባር ማምለክ ስላለብን) የሐዋ.24÷17፤ገላ.2÷10፤ያዕ.1÷27፡፡

ተግሣጽ

(አንድ ከጌታ መንገድ፣ከጌታ ሥርዓት፣ከጌታ ቃልና ፍቃድ (ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት) የወጣን ወገን፡በፍቅርና በትህትና ማረምማቅናት ፣መመለስና ጤናማ መንፈሳዊ ሕይወትን እንደገና እንዲቀጥል ማገዝ/ማስቻል ነው፡፡) ገላ. 6÷12ኛጢሞ.4÷2ዕብ.12÷411፡፡

 የአምላኬን ቤት ስለወደድሁ  ወርቅና ብር ለአምላኬ ቤት ሰጥቼዋለሁ !!

– 1ኛ ዜና 29፥3